ተስፋይ ገብርአብ ሃብተጽየን በሻዕቢያዎች ፓልቶክ እንግዳ ኾኖ በመቅረብ ያደረገው ውይይት ለትውውቅ ያክል ከተናገረው የተወሰደ (በትግርኛ) ስሜ ተስፋይ ገብረአብ እባላለሁ። ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሾፍቱ በምትባል መንደር ተወለጄ፣ አደግኩ። ቤተሰቦቼ ኤርትራዊያን ናቸው። አሁን የምኖረው ኤርትራ ውስጥ ባጽዕ እና ደንጎሎ አከባቢ ነው። መጻሕፍት እየጻፍኩ ነው የምኖረው። full time ጸሐፊ ነኝ። አሁን OSA (Oromo Studies Association) በሚባል ማህበር ባዘጋጀው ኮንፈረንስ ንግግር እንዳደርግ ጋብዞኝ ነው ወደ አሜሪካ ዋሽንግቶን ዲሲ፣ አሜሪካ የመጣሁት። በቅርብ ወደ አሥመራ እመለሳለሁ። በቅርብ ጊዜ የታተመችው የጀሚላ እናት የምትል መጽሐፌን ጨምሮ ሰባት መጻሕፍቶች አሳትምያለሁ።
Posted on: Tue, 14 Oct 2014 20:56:09 +0000
Trending Topics
Recently Viewed Topics
© 2015