መዝሙረ ዳዊት 65 Ps 65 1 አቤቱ፥ በጽዮን - TopicsExpress



          

መዝሙረ ዳዊት 65 Ps 65 1 አቤቱ፥ በጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል፥ ለአንተም ጸሎት ይቀርባል። 1 Praise waiteth for thee, O God, in Sion: and unto thee shall the vow be performed. 2 ሥጋ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል። 2 O thou that hearest prayer, unto thee shall all flesh come. 3 የዓመፃ ነገር በረታብን ኃጢአታችንንስ አንተ ይቅር ትላለህ። 3 Iniquities prevail against me: as for our transgressions, thou shalt purge them away. 4 አንተ የመረጥኸው በአደባባዮችህም ለማደር የተቀበልኸው ምስጉን ነው ከቤትህ በረከት እንጠግባለን። 4 Blessed is the man whom thou choosest, and causest to approach unto thee, that he may dwell in thy courts: we shall be satisfied with the goodness of thy house, even of thy holy temple. 5 ቤተ መቅደስህ ቅዱስ ነው በጽድቅም ድንቅ ነው። በምድር ዳርቻ ሁሉና በሩቅ ባሕር ውስጥ ላሉ ተስፋቸው የሆንህ፥ አምላካችንና መድኃኒታችን ሆይ፥ ስማን። 5 By terrible things in righteousness wilt thou answer us, O God of our salvation; who art the confidence of all the ends of the earth, and of them that are afar off upon the sea: 6 በጉልበትህ ተራሮችን አጸናሃቸው፥ በኃይልም ታጥቀሃል። 6 Which by his strength setteth fast the mountains; being girded with power: 7 የባሕሩን ጥልቀት የሞገድንም ጩኸት ታናውጣለህ። 7 Which stilleth the noise of the seas, the noise of their waves, and the tumult of the people. 8 ከተአምራትህ የተነሣ አሕዛብ ይደነግጣሉ፥ በምድር ዳርቻም የሚኖሩ ይፈራሉ የጥዋትንና የማታን መውጫ ደስ ታሰኛቸዋለህ። 8 They also that dwell in the uttermost parts are afraid at thy tokens: thou makest the outgoings of the morning and evening to rejoice. 9 ምድርን ጐበኘሃት አጠጣሃትም፥ ብልጥግናዋንም እጅግ አበዛህ የእግዚአብሔርን ወንዝ ውኃን የተመላ ነው ምግባቸውን አዘጋጀህ እንዲሁ ታሰናዳለህና። 9 Thou visitest the earth, and waterest it: thou greatly enrichest it with the river of God, which is full of water: thou preparest them corn, when thou hast so provided for it. 10 ትልምዋን ታረካለህ፥ ቦይዋንም ታስተካክላለህ በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ፥ ቡቃያዋንም ትባርካለህ። 10 Thou waterest the ridges thereof abundantly: thou settlest the furrows thereof: thou makest it soft with showers: thou blessest the springing thereof. 11 በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። 11 Thou crownest the year with thy goodness; and thy paths drop fatness. 12 የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ፥ ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ። 12 They drop upon the pastures of the wilderness: and the little hills rejoice on every side. 13 ማሰማርያዎች መንጎችን ለበሱ፥ ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉም። 13 The pastures are clothed with flocks; the valleys also are covered over with corn; they shout for joy, they also sing.
Posted on: Fri, 28 Mar 2014 04:08:57 +0000

Trending Topics



Recently Viewed Topics




© 2015