Al Jazeera - Ethiopian Migrants in Yemen Allege Torture - - TopicsExpress



          

Al Jazeera - Ethiopian Migrants in Yemen Allege Torture - ሒዩማን ራይትስ ዎች በዛሬው ዕለት ያወጣው ሪፖርት ለሥራ ፍለጋ ወደ አረብ ሀገራት በሚሄዱ የኢትዮጵያና የአካባቢዋ ሀገራት ዜጎች ላይ በየመን የሚፈጸመውን ዘግናኝ ማሰቃየትና ግድያ ይዘረዝራል፡፡ ባለ 82 ገጹ ሪፖርት በብዛት ከኢትዮጵያ ሳዑዲ አረቢያ ለመግባት በየመን አቋርጠው የሚሄዱ ዜጎች ላይ በማሰቃያ ካምፖች የሚደርስባቸውን አሰቃቂ ድብደባና ግድያ ቁልጥ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ በጀልባ የመን የሚገቡትን እየያዙ በካምፖቹ ውስጥ የሚያጉሩት የወንጀለኛ ቡድኖች ስደተኞቹን በማሰቃየትና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ይህን ያህል ብር ካላመጣችሁ እንገድላቸዋለን በሚል ማስፈራሪያ ብር እንደሚቀበሏቸው ይዘረዝራል ሪፖርቱ፡፡ በዚህ መልኩ ከአንድ ተያዥ ከ200 እስከ 1 300 ዶላር ድረስ ወንጀለኞቹ እንደሚቀበሉ ተገልጿል፡፡ አሰቃቂ ድብደባ፣ ጆሮ ማቃጠል፣ ጥፍር መንቀል፣ አስገድዶ መድፈርና ሌሎች እጅግ ሰቅጣጭ ማሰቃያዎች እንደሚፈጸሙ የሚጠቅሰው ሪፖርቱ የወንጀለኞቹ ቡድን ከሀገሪቱ ፖሊስና የጸጥታ ኃይል ጋር ያለውን መመሳጠርም ይጠቅሳል፡፡
Posted on: Tue, 27 May 2014 20:00:00 +0000

Trending Topics



Recently Viewed Topics




© 2015