Egypt: Presidential Runner Pledges to Peacefully Resolve Dam Row With Ethiopia ... See at ... diretu.be/766745 | አል ሲሲ ከተመረጥኩ አዲስ አበባ ሄጄ እደራደራለሁ አሉ፡፡ ግብጽ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እያካሄደች ባለችበት በዛሬው ዕለት ሱዳን ትሪብዩን ያወጣው አንድ ዘገባ በፕሬዝዳንታዊው ምርጫ እንደሚያሸንፉ ተስፋ የተጣለባቸው አብደል ፋታህ አል ሲሲ ከተመረጡ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ውጥረት ለማርገብ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው በድርድር እንደሚፈቱት ተናግረዋል፡፡ የአባይ ጉዳይ ለግብጽ የሞት ሽረት ጉዳይ ነው ባዩ አል ሲሲ ሀገራቸው ረግጣ ወደ ወጣችበት የሦስትዮሽ ድርድር ከመመለስ ውጪ በምን መልኩ አዲስ አበባ መጥተው በውይይት ሊፈቱት እንዳሰቡ ያሉት ነገር የለም፡፡ በብዙዎች ዘንድ ጉዳዩ የምርጫ ሰሞን ዲስኩር ከመሆን አይዘልም፡ የድሬትዩብ ወዳጆች በዚህ ጉዳይ ላይ ያላችሁን አስተያየት አድርሱን
Posted on: Wed, 28 May 2014 07:00:01 +0000
Trending Topics
Recently Viewed Topics
© 2015