Ethiopias female filmmakers make an impact ... See at ... diretu.be/822487 | በኢትዮጵያ የፊልም ኢንደስትሪ የሴት ፊልም ሰሪዎች ሚና እያደገ ነው ተባለ የኢትዮጵያ ፊልም ኢኒሼቲቭ መስራች የሆነችው ስዊድናዊቷ ራግነሂልድ ኢኬ እንዳለችው ከሆነ በኢትዮጵያ ሴት የፊልም ሰሪዎች ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ ለዚህም በ International Emerging Film Talent Association በሚዘጋጀው ካንስ የፊልም ፌስቲቫል ላይ በየአመቱ እየተሳተፉ እና ለመሳተፍ እያመለከቱ የሚገኙ ሴት የፊልም ዳይሬክተሮችን እና የፊልም ባለሞያዎችን ዋቢ አድርጋለች፡፡ ከ30 እስከ 40 ከሚሆኑት የፊልም ፌስቲቫሉ አመልካች የፊልም ዳይሬክተሮች አብዛኞቹ ሴት የፊልም ባለሞያዎች መሆናቸው በኢትዮጵያ የፊልም ኢንደስትሪ ላይ የሴቶች ሚና እና ተጽእኖ ፈጣሪነትን የሚያመለክት እንደሆነም ተጠቅሷ፡፡ በኢትዮጵያ በሲኒማ ቤት እየታዩ ካሉ እና ከፍተኛ ተመልካች ለማግኘት ከቻሉ ፊልሞች ውስጥም በሴቶች ዳይሬክት የተደረጉ ፊልሞች በርካታ ናቸውም ተብሏል፡፡ ለዝርዝሩ .... diretu.be/822487
Posted on: Fri, 30 May 2014 09:00:00 +0000